በልደታ ክ/ከተማ የሴቶች፣ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ዝርዝር አገልግሎቶች

1. ለሴቶች የማህበራዊ አገልግሎት ድጋፍ መስጠት፣
  • ከፍለው መማር ለማይችሉ ሴቶች የትምህርት እድልና ድጋፍ ማመቻቻት፣
  • በጎልማሶች ተግባር ተኮር ትምህርት ማሳተፍ፣
  • የነፃ ህክምና ድጋፍ እንዲያገኙ ማመቻቸት፣
2. ሴቶችን በገቢ ማስገኛ ዘርፎች እንዲሰማሩ ድጋፍ መስጠት፣
  • ተስማሚ ቴክኖሎጅዎችን ለተጠቃሚዎች ማሰራጨት፣
  • በቴክኖሎጅ ሽግግር ዙሪያ የሚከሰቱ ቅሬታዎችን መፍታት፣
  • ሴቶች የስራ እድል እንዲፈጠርላቸው ማመቻቸት፣
3. ሴቶች የብድርና ቁጠባ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሁኔታዎችን ማመቻቸት
  • የብድር አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማመቻቸት፣
  • የቁጠባ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማመቻቸት፣

4. ፆታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶችን መከላከልና ተግባራዊ ምላሽ መስጠት፣
  • ለጥቃት ተጎጅዎች ተግባራዊ ምላሽ መስጠት፣
  • ለሴት የመንግስት ሰራተኞች የትምህርት እድል ማመቻቸት፣
  • የህግና የስነ-ልቦና ምክር አገልግሎት እንዲያገኙ ማመቻቸት፣

5. አማራጭ የህፃናት ክብካቤ አገልግሎት መስጠት፣
  • ጉዲፈቻ አገልግሎት፣
  • አደራ ቤተሰብ አገልግሎት፣
  • የመልሶ ማቀላቀል አገልግሎት፣
  • መልሶ የማዋሀድ አገልግሎት መስጠት፣
  • የተቋም አገልግሎት መስጠት፣

6. ምክር፣ የምክክርና አመራር አገልግሎት መስጠት፣
  • ለህፃናት የስነ ልቦና ምክር አገልግሎት መስጠት፣
  • ለህፃናት ቤተሰብ ምክር አገልግሎት መስጠት፣

7. የአልሚ ምግቦችን ለእርጉዝ እናቶችና ጨቅላ ህፃናት አቅርቦትና ክትትል፣
  • የአልሚ ምግብ አቅርቦት ማመቻቸት፣
  • የአልሚ ምግብ አጠቃቀም ላይ ምክር መስጠት፣
8. ለህፃናት የቀን ማቆያ ማስፋፋትና ድጋፍ ማድረግ፣
  • የማህበረሰብ አቀፍ የህፃናት የቀን ማቆያ ማዕከላት ማቋቋምና መደራጀት፣
  • በመንግስት መስሪያ ቤቶች የህፃናት የቀን ማቆያ ማዕከላት እንዲቋቋሙ ድጋፍ ማድረግ፣

9. ተጠቃሚዎችን ከመሰረታዊ ማህበራዊ አገልግሎት ማስተሳሰር፣
  • ከባንክ ገንዘብ መቀበል የማይችሉ የቀጥታ ድጋፍ ተጠቃሚዎች ውክልና ማመቻቸት፣
  • ቅሬታ ማስተናገድ፣

10. ለተጠቃሚዎች የኑሮ ማሻሻያ አገልግሎት መስጠት፣
  • የጋራና የተናጠል የምክርና አመራር አገልግሎት መስጠት፣
  • ወደ ተቋማት የሚገቡ ተቋቋሚዎችን ለተቋማት ማስረከብ፣
  • ተቋቋሚዎችን ወደ ቤተሰብ መሸኘት፣፣
  • የስራ እድል ተጠቃሚ ማድረግ፣

11. ለከፋ የማህበራዊ ችግር ውስጥ ለገቡ የህብረተሰብ ክፍሎች ማህበራዊ ድጋፍ ማድረግ፣
  • ለከፋ የምግብ ችግር የተጋለጡ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ማድረገ፣፣
  • ተጠቃሚዎችን ከማህበረሰብ አቀፍ ድጋፍና ክብካቤ ጥምረቶች ጋር ማስተሳሰር፣፣

12. ለእድሮች የምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት መስጠት፣
  • ለእድር ምክር ቤቶች የፈቃድ እድሳት መስጠት፣፣
  • ለእድር ምክር ቤቶች አዲስ ፈቃድ መስጠት፣

13. የአካል ጉዳተኞችና አረጋውያን ጉዳይ አካቶ ትግበራን ማስፈጸም፣
  • አካል ጉዳተኞች የነፃ ትምህርት እድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ማመቻቸት፣
  • የህግና ምክር ድጋፍ አገልግሎት መስጠት፣
  • አምራች አካል ጉዳተኘችና አረጋውያን ለምርቶቻቸው ማሳያና መሸጫ ኤግዚብሽንና ባዛር ማዘጋጀት፣
14. ለአካል ጉዳተኞችና አረጋውያን የተሃድሶ አገልግሎት መስጠት፣፣
  • የተቋም አገልግሎት መስጠት፣
  • የስራ ቅጥር ተጠቃሚ ማድረግ፣

15. የሰው ሰራሽ አካልና አካል ድጋፍ አገልግሎት ማመቻቸት፣
  • የምክርና አመራር አገልግሎት መስጠት፣
  • አቅም ለሌላቸው አካል ጉዳተኞችና አረጋውያን የነፃ ህክምና/ የጤና መደህን አገልግሎት ማመቻቸት፣
  • አቅም ለሌላቸው አካል ጉዳተኞች የአካል ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግ፣
  • አቅም ለሌላቸው አካል ጉዳተኞች የሰው ሰራሽ የአካል ድጋፍ እንዲያገኙ ማድረግ፣ ፣

16. መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን ፕሮጀክቶች ማበልፀግ፣

17. የበለፀጉ ፕሮጀክቶችን ክትትልና ድጋፍ ማድረግ፣
  • የፕሮጀክት አማካይ አፈፃፀም ግምገማ ማካሄድ፣
  • የፕሮጀክት ማጠናቀቂያ ግምገማ ማካሄድ፣
  1. ገጽ-1
  2. ገጽ-2